Tuesday, July 22, 2014

እውቀት


ፒያጌት የተባለች ሳይኮሎጂስት፡ እውቀት ሁሉም ጋር ይገኛል ትለናለች ማለትም ህፃናትም ጋር አዋቂዎችም ጋር ነገር ግን ልዩነቱ የመጠን፣ የጥልቀት እና የብዛት ነው ትላለች፡፡ እድሜና ጊዜ አያስተምርም አይባልም ያስተምራል ግን ስንቶቻችን አይናችንን ገልጠን ጆሯችንን ከፍተን እጃችንን ዘርግተን አፍንጫችንን አፈንጭተን፣ ምላሳችንን አውጥተን እውቀት እንቀምሳለን? ነው ጥያቄው በተለይ ደግሞ በአዋቂዎች ስም ተጠርተን በዛ ደረጃ የምንገኝ ሰዎች በዚያ ዘርፍ መገኘት ብቻውን እውቀት ይመስል ህፃናትን እንወቅሳለን በሌሎች ከኛ በእድሜ ባነሱ ሰዎች እናፌዛለን፡፡ አንድ የአራት አመት ህፃን ልጅ አባቱን ሊያውቅ ይችላል እናቱን በደንብ ይለያል ነገር ግን አያቶቹን ቅድመ አያቶቹንና ቅማት ምዝላቶቹን ላያውቅ ይችላል ይህ የሚያመለክተው የልጁን የእውቀት ጥልቀት እጥረትና ማነስ ነው እንጂ የልጁን አለማወቅ አይደለም ምክኒያቱም ቢያንስ ከቤተሰቡቹ የመጀመሪያዎቹንና ዋነኞቹን አውቋልና፡፡ ወላጆቹ ግና ከነ ዘር ማንዘራቸው አበቃቀል ከነ አመጣጣቸውና አስተዳደጋቸው ያውቃሉ ይህም በአንድ ቀን የመጣ ታምር አይደለም ሲጠይቁ ሲፈትሹ በህይወት ኑረው ያወቁት ነው፡፡ ህፃን ትልቁን ሰው እሚበልጥበት ብዙ ነገር አለው እንዲሁም ትልቁ ህፃኑን እሚበልጥበት ብዙ ዘርፍ አለው፡፡ ለምሳሌ ህፃን ልጅ ቂም አይዝም እሚናገረውም በቀጥታ ነው እሚናገረውን ነው እሚሆነው እንዲሁም የዋህ ነው ነገር ግን ትልቁ ሰው ቂም ይይዛል ሁሌም ፍልስፍና አይሉት ቅኔ አዙሮ ማሰብ ይወዳል ቀጥተኛ ሀሳብም የለው የዋህነትም ይጎድለዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ይህ የሁለቱ የህይወት ጎራ ሁል ጊዜም የህፃኑ ባህሪ ለራሱ አይጠቅመውም ሁልጊዜም አይጎዳውም፣ በተመሳሳይ ለትልቁም ሰው እንዲሁ ይህ እንዲሆን ያደረገው ደግሞ ያለን የህይወት ወይንም የነገሮች እውቀት መጠንና ጥልቀት እንጂ ፍፁም አለማወቅ አይደለም እንደውም ፕላቶ እንደሚለው የሰው ልጅ በተፈጥሮ አላዋቂ አይደለም አብሮት የተወለደ አንዳች ማወቂያና እውቀት አለው እንጂ፡፡

No comments:

Post a Comment